Tuesday, January 5, 2021

የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል

 ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።

ብፁዕነታቸው በዓሉን አስመልክተው ያስተላለፉት የእንኳን አደረችሁ ሙሉ መልእክት እነሆ!

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ወናሁ እዜንወክሙ ዐቢየ ፍስሐ ዜና ዘይከውን ለኩሉ ዓለም
ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁ፡፡
ሉቃ2÷10

የተወደዳችሁ በሀገር ውስጥ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ከሀገር ውጪ የምትኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ኦርቶዶክሳውያንና ኦርቶዶክሳውያት በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የ2013 በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡

የተወደዳችሁ ክርስቲያኖች እንደሚታወቀው አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ በአርአያውና በአምሣሉ ፈጥሮ በልጅነት አክብሮ ቦታ ቢሉ ገነት ክብር ቢሉ ልጅነት አጐናፅፎ በዚህ አለም ሲኖር ስሙን አመስግኖ በወዲያኛው ዓለም ክብሩን እንዲወርስ ቢታደልም የሰው ልጅ ግን አደርግ የተባለውን ትቶ አታድርግ የተባለውን በማድረጉ ከፀጋ እግዚአብሔር እና ከልጅነት ክብር ተራቁቶ ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በግብርናተ ዳያቢሎስ ተይዞ የጨለማ ግርዶች ተጋርዶበት በመከራ ድንኳን በለቅሶና በሐዘን ሲኖር ግድ ሆኖበታል፡፡

ደጋግ የእግዚአብሔር ሰዎች ቅዱሳን እንኳን ሳይቀሩ ምንም እንኳን ሲኦልም ወርደው በረዴተ እግዚአብሔር ተጠብቀው ስቃይ መከራ ባያገኛቸውም የሕይወት እድል ፈንታቸው ግን ወደ ሲኦል መውረድ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን አይደለም ነውራቸው ሐጢአታቸው ይቅርና ጽድቃቸው እንኳን እንደመርገም ጨርቅ የሚቆጠርበት ዘመን ነበረ፡፡

ሆኖም ግን ጥንታዊው ሰው አባታችን አዳም ትዕዛዘ እግዚአብሔርን አፍርሶ ምክረ ሰይጣንን ሰምቶ በላቡና በወዙ እንዲበላ ተፈርዶበት ወደ ምድር ሲመጣ በደሙ ለውሶ እግዚአብሔር ይቅር ይለው ዘንድ መስዋዕት ቢያቀርብ አምላካችን እግዚአብሔር ዓለም የሚድነው በእግዚአብሔር ልጅ ደም እንጂ በሰው ደም አይደለም ብሎ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በሜዳህ ድኬ በመስቀል ላይ ተሰቅዬ ሞቼ አድንሃለሁ ብሎ የማይታበል ፅኑ ቃል ኪዳን ገብቶለት ነበርና ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ የቀጠሮው ዘመን በደረሰ ጊዜ አንድ ልጁን ላከ ከሴትም ተወለደ፡፡ በገላ 4÷4

እንዳለው ቃል ኪዳን የገባበት ዘመን ሲደርስ ከዘመኑ ዘመን ከዓመቱ ዓመት ከወርሁ ወር ከዕለቱ ዕለት ከሰዓቱ ሰዓት ሳያሳልፍ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማሪያም ፍፁም አምላክ ፍፁም ሰው ሆኖ በዛሬው ዕለት ተወልዶልናል በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጊዜው የሚወለድበት ስፍራ አቶ ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ ሁሉ የእርሱ የሆነለት በሁሉ ባለፀጋ ሲሆን ስለ ሰው ልጅ ፍቅር በሁሉ ደሃ ሆኖ በከብት ግርግም ተወለደልን፡፡

ሰማይን በከዋክብት ምድርንም በአበባ የሚያስጌጥ ጌታ እንዲሁም እናቱ ሐርና ወርቅን እያስማማች የምትፈትል ስትሆን የሚለብሰው አጥቶ በለሶን የተባለ ቅጠል እናቱ አልብሰዋለች፡፡

በተወለደም ዕለት በአካባቢው በለሊት ተግተው መንጋቸውን ይጠብቁ ወደነበሩ እረኞች የጌታ መልአክ ቀርቦ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድሃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል፡፡

ለዚህም ምልክት እስከ ቤቴልሄም ሂዱ ሕፃኑን ከእናቱ ጋር በከብት ግርግም ተኝቶ ታገኙታላችሁ ብሎ ምልክት ነግሯቸው መጥተው ከእናቱ ጋር አግኝተውት አመስግነውታል፡፡ በዚህም ዕለት ተጣልተው የነበሩ ሰው እና መልአክት ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ስምረቱ ለሰብ እያሉ በአንድነት እግዚአብሔርን አመስግነውታል፡፡

ከዚህ የተነሳ በጌታችን ልደት ሰው እና እግዚአብሔር ሰው እና መልአክት ሰው እና አራዊት ነፍስና ሥጋ ታርቀዋል፡፡ ታርቀውም በህብረት እግዚአብሔርን በታላቅ ምስጋና አመስግነውታል፡፡

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ይሄ በዓል አምላካችን እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ሲል ሰባቱን ሰማያት ትቶ በከብት በረት ዝቅ ብሎ ትሕትናን ያሳየበት በመሆኑ ሁላችንም ከአምላካችን ትሕትና በመማር የትሕትና ሰው ልንሆን ያስፈልጋል፡፡

እንዲሁም በሁሉም ዘንድ እርቅ ፣ ሠላም ፍቅር አንድነት ለሰው ልጅ ሁሉ የተመሰረተበት የእርቅ ቀን በመሆኑ ሁላችንም የሰላ የፍቅር የእርቅ ልብ ገዝተን በዓሉ በሚጠይቀው ሃይማታዊ ሥርዓትና ፀባይ ልናከብረው ይገባል፤ በተለይ በዚህ በዓል ሰው መሆንን መማር ያስፈልጋል፡፡

ምክንያቱም ሰው መሆን ከምንም ከምን ይቀድማልና ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዚህ ነው ሰው ሆኖ ሰው ያደረገን በተለይም አሁን በአለንበት ዘመን ፍቅር ሰላም መተሳሰብ ኩላችንም ሕይወት የጐደለ በመሆኑ ይህንን የጐደለንን የኢትጵያዊነት መገለጫ መልሰን ገንዘባችን ልናደርገው ያስፈልጋል።

በተለይም ለበዓሉ ለሥጋችን የሚያስፈልገንን የሥጋ ገበያ እንደምናሟላ ሁሉ ለነፍሳችን የሚያስፈልጋትን የነፍስ ገበያ ማለትም ፍቅር ይቅርታ ሰላም በመገብየት ሥጋና ደሙን በመቀበል በፍፁም የሰላ መንፈስ በመመራ በዓላችንን ከምንጊዜውም በላይ ልናከብረው ያስፈልጋል፡፡

በዓሉን ስናከብር ለተራበ በማብላት ለተጠማ በማጠጣት ለተራቆተ በማበስ በአጠቃላይ በማካፈል እንዲሆን ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።

ብፁዕነታቸው በዓሉን አስመልክተው ያስተላለፉት የእንኳን አደረችሁ ሙሉ መልእክት እነሆ!

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ወናሁ እዜንወክሙ ዐቢየ ፍስሐ ዜና ዘይከውን ለኩሉ ዓለም
ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁ፡፡
ሉቃ2÷10

የተወደዳችሁ በሀገር ውስጥ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ከሀገር ውጪ የምትኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ኦርቶዶክሳውያንና ኦርቶዶክሳውያት በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የ2013 በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡

የተወደዳችሁ ክርስቲያኖች እንደሚታወቀው አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ በአርአያውና በአምሣሉ ፈጥሮ በልጅነት አክብሮ ቦታ ቢሉ ገነት ክብር ቢሉ ልጅነት አጐናፅፎ በዚህ አለም ሲኖር ስሙን አመስግኖ በወዲያኛው ዓለም ክብሩን እንዲወርስ ቢታደልም የሰው ልጅ ግን አደርግ የተባለውን ትቶ አታድርግ የተባለውን በማድረጉ ከፀጋ እግዚአብሔር እና ከልጅነት ክብር ተራቁቶ ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በግብርናተ ዳያቢሎስ ተይዞ የጨለማ ግርዶች ተጋርዶበት በመከራ ድንኳን በለቅሶና በሐዘን ሲኖር ግድ ሆኖበታል፡፡

ደጋግ የእግዚአብሔር ሰዎች ቅዱሳን እንኳን ሳይቀሩ ምንም እንኳን ሲኦልም ወርደው በረዴተ እግዚአብሔር ተጠብቀው ስቃይ መከራ ባያገኛቸውም የሕይወት እድል ፈንታቸው ግን ወደ ሲኦል መውረድ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን አይደለም ነውራቸው ሐጢአታቸው ይቅርና ጽድቃቸው እንኳን እንደመርገም ጨርቅ የሚቆጠርበት ዘመን ነበረ፡፡

ሆኖም ግን ጥንታዊው ሰው አባታችን አዳም ትዕዛዘ እግዚአብሔርን አፍርሶ ምክረ ሰይጣንን ሰምቶ በላቡና በወዙ እንዲበላ ተፈርዶበት ወደ ምድር ሲመጣ በደሙ ለውሶ እግዚአብሔር ይቅር ይለው ዘንድ መስዋዕት ቢያቀርብ አምላካችን እግዚአብሔር ዓለም የሚድነው በእግዚአብሔር ልጅ ደም እንጂ በሰው ደም አይደለም ብሎ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በሜዳህ ድኬ በመስቀል ላይ ተሰቅዬ ሞቼ አድንሃለሁ ብሎ የማይታበል ፅኑ ቃል ኪዳን ገብቶለት ነበርና ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ የቀጠሮው ዘመን በደረሰ ጊዜ አንድ ልጁን ላከ ከሴትም ተወለደ፡፡ በገላ 4÷4

እንዳለው ቃል ኪዳን የገባበት ዘመን ሲደርስ ከዘመኑ ዘመን ከዓመቱ ዓመት ከወርሁ ወር ከዕለቱ ዕለት ከሰዓቱ ሰዓት ሳያሳልፍ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማሪያም ፍፁም አምላክ ፍፁም ሰው ሆኖ በዛሬው ዕለት ተወልዶልናል በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጊዜው የሚወለድበት ስፍራ አቶ ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ ሁሉ የእርሱ የሆነለት በሁሉ ባለፀጋ ሲሆን ስለ ሰው ልጅ ፍቅር በሁሉ ደሃ ሆኖ በከብት ግርግም ተወለደልን፡፡

ሰማይን በከዋክብት ምድርንም በአበባ የሚያስጌጥ ጌታ እንዲሁም እናቱ ሐርና ወርቅን እያስማማች የምትፈትል ስትሆን የሚለብሰው አጥቶ በለሶን የተባለ ቅጠል እናቱ አልብሰዋለች፡፡

በተወለደም ዕለት በአካባቢው በለሊት ተግተው መንጋቸውን ይጠብቁ ወደነበሩ እረኞች የጌታ መልአክ ቀርቦ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድሃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል፡፡

ለዚህም ምልክት እስከ ቤቴልሄም ሂዱ ሕፃኑን ከእናቱ ጋር በከብት ግርግም ተኝቶ ታገኙታላችሁ ብሎ ምልክት ነግሯቸው መጥተው ከእናቱ ጋር አግኝተውት አመስግነውታል፡፡ በዚህም ዕለት ተጣልተው የነበሩ ሰው እና መልአክት ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ስምረቱ ለሰብ እያሉ በአንድነት እግዚአብሔርን አመስግነውታል፡፡

ከዚህ የተነሳ በጌታችን ልደት ሰው እና እግዚአብሔር ሰው እና መልአክት ሰው እና አራዊት ነፍስና ሥጋ ታርቀዋል፡፡ ታርቀውም በህብረት እግዚአብሔርን በታላቅ ምስጋና አመስግነውታል፡፡

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ይሄ በዓል አምላካችን እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ሲል ሰባቱን ሰማያት ትቶ በከብት በረት ዝቅ ብሎ ትሕትናን ያሳየበት በመሆኑ ሁላችንም ከአምላካችን ትሕትና በመማር የትሕትና ሰው ልንሆን ያስፈልጋል፡፡

እንዲሁም በሁሉም ዘንድ እርቅ ፣ ሠላም ፍቅር አንድነት ለሰው ልጅ ሁሉ የተመሰረተበት የእርቅ ቀን በመሆኑ ሁላችንም የሰላ የፍቅር የእርቅ ልብ ገዝተን በዓሉ በሚጠይቀው ሃይማታዊ ሥርዓትና ፀባይ ልናከብረው ይገባል፤ በተለይ በዚህ በዓል ሰው መሆንን መማር ያስፈልጋል፡፡

ምክንያቱም ሰው መሆን ከምንም ከምን ይቀድማልና ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዚህ ነው ሰው ሆኖ ሰው ያደረገን በተለይም አሁን በአለንበት ዘመን ፍቅር ሰላም መተሳሰብ ኩላችንም ሕይወት የጐደለ በመሆኑ ይህንን የጐደለንን የኢትጵያዊነት መገለጫ መልሰን ገንዘባችን ልናደርገው ያስፈልጋል።

በተለይም ለበዓሉ ለሥጋችን የሚያስፈልገንን የሥጋ ገበያ እንደምናሟላ ሁሉ ለነፍሳችን የሚያስፈልጋትን የነፍስ ገበያ ማለትም ፍቅር ይቅርታ ሰላም በመገብየት ሥጋና ደሙን በመቀበል በፍፁም የሰላ መንፈስ በመመራ በዓላችንን ከምንጊዜውም በላይ ልናከብረው ያስፈልጋል፡፡

በዓሉን ስናከብር ለተራበ በማብላት ለተጠማ በማጠጣት ለተራቆተ በማበስ በአጠቃላይ በማካፈል እንዲሆን በእግዚአብሔር ቃል ማሳሰብ እፈልጋለሁ፡፡

በመጨረሻም በዓሉ ክፉ ነገር የማሰማበት ክፉ ነገር የማናይበት በጐ በጐ ነገር የምንሰማበትና የምናይበት የተራቡ የሚጠግቡበት የተጠሙ የሚረኩበት የታሰሩ የሚፈቱበት የተጨነቁ የሚያርፉበት በዓል ይሆንልን ዘንድ በፅኑ እመኛለሁ፡፡

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/መ//ፓ/ጠ/ጽ/ቤት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
27/04/2013 ዓ/ም
ሰሜን ሸዋ ደብረ ብርሃን ኢትዮጵ
join t.me/eotcnsd